መጪው ጊዜ ከዐብይ ጋር!

መንግሥት በሽብርተኝነት ለፈረጃቸው ተቃዋሚ ቡድኖች የሽብርተኝነት ፍረጃውን በማንሳት ትልቅ ርምጃ ወስዷል፡፡ ጸረ-ሽብር ሕግ አንስቶ የምህረት አዋጅ አጽድቋል፡፡ ይህንኑ ርምጃ ተከትሎ በሽብር ተከሰው የነበሩ ፖለቲካ ቡድኖች ወደ ሀገራቸው እንዲገቡ ጥሪ አድርጓል፡፡ በሌላ በኩል ብሄርተኞች የክልልነት፣ የሙስሊም መብት ተሟጋቾች ደሞ ነባር ጥያቄያቸውን እያሰሙ ያሉት ለውጡን ለመጠቀም ነው፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደሞ በውጭ ሀገራት ያሉ የተቃራኒ ፖለቲካ ቡድኖች ጠቅላይ ሚንስትሩ ያቀረቡትን ጥሪ ተቀብለው ወደ ሀገር መግባታቸውን በበጎ የሚያዩት እንዳሉ ሁሉ በስጋት የሚያዩትም ወገኖች አልጠፉም፡፡ እናም ቡድኖቹ ተቃራኒ ፍላጎቶቻቸውን እና ፖለቲካዊ አጀንዳዎቻቸውን በምን መልኩ ያንጸባርቁ ይሆን? ቡድኖቹ ባንድ ጊዜ መሰባሰባቸው ለሀገሪቷ ምን ዐይነት ትሩፋት እና ስጋት ይፈጥር ይሆን? ሁኔታው በጠቅላላው ምን ዐይነት ቅራኔዎችን እና ግጭቶችን ሊፈጠር ይችላል?

ዶ/ር አብይ አህመድ ከኃይለማርያም ደሳለኝ በምን ይለያሉ?

በተለይ ዶክተር አብይ እንደ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ሁሉ የግንባሩ አስኳል ከሆነው ሕወሃት ውጭ የተመረጡት ስለሆኑ ለሩብ ክፍለ ዘመን ጭቆና የመረረውን ሕዝብ ወደ ቃል ኪዳኗ ምድር የሚያደርሱ ሐዋሪያ አድርጎ ማየት በምንም መልኩ የሚያዋጣ አይደለም፡፡

ኦቦ ለማና ህወሃት

አቶ ለማ መገርሳ የመንግስት ባለስልጣን ሆኖ በቆየበት ጊዜ ሁሉ ሲያስገድል፣ በሀሰት ሲያስወነጅል፣ ሕዝብን ከሕዝብ ሲያባላ እና በድህነት እንድንሰቃይ ለሙስና ሲያጋፍር ነው የኖረው። ሌላውን የኢህአዴግ ባለስልጣን አስኮንኖ፣ አቶ ለማ እና ዶ/ር ዐብይን ነጻ የሚያስወጣ ምንም ዓይነት ምክንያት የለንም። ማሽሞንሞን ሳያስፈልግ፥ አቶ ለማ መገርሳ የኢህአዴግ ሽንት ጨርቅ ነው። የአምባገነን ስርዓት ሽንት እንዳይታይ በማድረግ ረገድ የሚጫወተው የዳይፐርነት ሚና... Continue Reading →

ከደርግ ወደ ጎሣዊ ደርግ- “ግንቦት 20” (ክፍል ፮)

የአንድ ጎጥ የበላይነትና የመበታተን አደጋ! ራሳቸውን “የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር” ብሎ በመሰየም የትግራይን ሕዝብ ሽፋን በማድረግ፤ “የምታገለው ለአንተ ነጻነት ነው” በማለት፤ መልሶ እታገልለታለሁ ያለውን ሕዝብ ያስጨፈጨፈው፣ ያስራበው፣ የግፈ ሰለባ ያስደረገው፣ … ራሱን ህወሓት እያለ የሚጠራው የወንበዴዎች ቡድን የኢትዮጵያን የሥልጣን መንበር ከተቆናጠጠ በኋላ የትግራይ ሰዎችን በሌላው ኢትዮጵያዊ ለማስጠላትና “ስም ለማሰጠት” እንዲሁም ለማጠልሸት ባለፉት 26ዓመታት ሲሰራ... Continue Reading →

ከደርግ ወደ ጎሣዊ ደርግ- “ግንቦት 20” (ክፍል ፬)

የመንግስት ውሸትና የሃይማኖት ተቋማት ውድቀት የትግራይ ሕዝብ “ነጻ አውጡኝ” ብሎ ሳይሰይማቸው፣ ሳይመርጣቸው፣ ሳይጠይቃቸው፣ ራሳቸውን “የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር” ብለው የሰየሙ ወንበዴዎችና ሽፍቶች የምኒልክ ቤተመንግሥት ከገቡ 26 ዓመታት ተቆጥረዋል። በቂም፣ በበቀል፣ በክፋትና በኢሞራላዊ ተግባራት የተሞሉ፤ ኢትዮጵያዊ መሆናቸው ፈጽሞ የሚያጠራጥር፤ ማንነታቸው ይህ ነው ተብሎ የማይታወቅ፤ በሐሰት ስም ከበረሃ እስከ ቤተመንግሥትና ዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የታዩ፤ በሐሰት ፕሮፓጋንዳ... Continue Reading →

ከደርግ ወደ ጎሣዊ ደርግ- “ግንቦት 20” (ክፍል ፫)

ስደት በመጀመሪያው ከደርግ ወደ ጎሣዊ ደርግ- “ግንቦት 20” (ክፍል ፩) ጽሑፍ ከ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች መሃል ስለከሸፈው የፌዴራል ሥርዓት እና የትምህርት ፖሊሲው ክስረት ማተታችን ይታወሳል። በሁለተኛው ክፍል ሰለ መሬት ነጠቃ አስነብበናል በዚህኛው ክፍል ሁለት ደግሞ የአፓርታይዳዊ አገዛዝ አራማጁ ህወሓት ሥልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ከዘራቸው በርካታ መርዛማ ፍሬዎች መካከል ቀጣዩን ከማሳያዎች ጋር ማስነበባችን እንቀጥላለን። መርዛማ ፍሬ 4፡ ስደት የኢትዮጵያዊያን... Continue Reading →

ከደርግ ወደ ጎሣዊ ደርግ- “ግንቦት 20” (ክፍል ፪)

የመሬት ነጠቃ በረዥሙ የኢትዮጵያ ታሪክ በአስተዳደሩ ተመስግኖ በክብር የተሸኘ ገዥ ስለመኖሩ የሚያወሳ ታሪከ-ድርሳን ፈልጎ ማግኘት የሚቻል አይመስልም። ሁሉም አገዛዞች የተወገዱት በአመፅ አልያም በተፈጥሮ ሞት ነው። ልክ የዛሬ 26 ዓመት 1983 ዓ.ም. ወርሃ ግንቦት በምዕራቡ አለም ረዳትነት በጠመንጃ ወደ ሥልጣን የመጣው አፓርታይዳዊው የህወሓት ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ በቀደሙት ገዥዎች የብረት ጫማ ውስጥ ተከልሎ አፈናና ግድያውን “ግፋ በለው!”... Continue Reading →

ከደርግ ወደ ጎሣዊ ደርግ- “ግንቦት 20” (ክፍል ፩)

ፌዴራሊዝምና የትምህርት ፖሊሲ ግንቦት ሃያ ባይኖርስ ኑሮ፥ የደርግ ዘመን ቀጥሎ ቢሆን ኑሮ ላልፉት ሩብ ምዕት ዐመታት ኢትዮጵያ ምን ትመስል ነበር እያልኩ አስባለው። የግንቦት ሃያ ህልም ቅዠት በነበረ፥ ባለቁምጣዎች ቤተ መንግስትን ለመቀመጫቸው የ''ሰፊውን ሕዝብ'' ንብረት ለጎፈሬያቸው ማስዋቢያ ባያደርጉት በነበረ፥ የሃያ ስድስት ዓምት ጆሮአችን በከሳ ኑሮ- ከአደንቁሩ ፕሮፓጋንዳ እያልኩ እያያሰላሰልኩ ሃሳቤን ከማስፈሬ አስቀድሞ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ የሠራውን ዘጋባ... Continue Reading →

የግንቦት ፍሬዎች ሁለት

የግንቦት ፍሬዎች ሁለት To Read in PDF ዘመነ ግንቦታውያን ከሰጡን ፍሬዎች መቅመስ ጀምረናል። የጎልማሳው ትውልድና የተተኪው ትርክት እንደቀጠለ ነው። ከፍሬዎቹ አንዱ በሆነው የዜግነት ክብር ላይ ዛሬ እንቆያለን። ከዚህ ቀደም በዚህ ርእስ ላይ ጽፌ ነበር። ይሄኛው ጽሑፍ ዝርዝር ዜናሁ ነው። ሰው በመሆን ጸጋና በጥቅሙ ደስታ አንድ ሆነን ተሰርተናል። በምንኖርበት ሥፍራ ባስቀመጥናቸውና በተቀመጡብን አለቃዎች ምክንያት ይህ የሰውነት... Continue Reading →

በታጋዮች ክንድ የደቀቀው ፍርድ

በታጋዮች ክንድ የደቀቀው ፍርድ – ታሪኩ አባዳማ ታጋዩ አቶ በረከት ስምኦን ሲኖሩበት ከነበረ ንብረትነቱ የአቶ መሀሪ ተወልደ ብርሀን የሆነ የተንጣለለ ቪላ ለቀው እንዲወጡ እና ለባለንብረቱ እንዲያስረክቡ ፍርድ ቤት ቢወስንም ለሳቸው የሚመጥን ሌላ ቤት ባለመገኘቱ ውሳኔው ተፈፃሚ ሊሆን አልቻለም። ቤቱ ለባለንብረቱ እንዲመለስ ላለፉት ስምንት አመታት በተከታታይ በህግ ቢወሰንም ከህግ በላይ የሆነ ሰው ስለሚኖርበት ተፈፃሚ አልሆነም –... Continue Reading →

Start a Blog at WordPress.com.

Up ↑